ዶክተሮች አትድንም ብለውኝ ነበር

ወንድማችን ወጣት ዳኛው አዳነ ይባላል፡፡የመጣው ከጸገዴ ወረዳ ሲሆን በወንቅ እሸት ገዳም በእግዚአብሔር ቸርነት በአባ ዮሐንስ ተስፋ ማርያም ጸሎት የተደረገለትን ተአምር እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ እኔ ለ4 ዓመት ሙሉ በጣም ከባድ በሆነ የእግር ህመም በሽታ ተይዠ ስሰቃይ ኖሬያለሁ፡፡እግሬ ፈጽሞ አይታጠፍም፤ከእግሬም ንጹህ ደም ሁልጊዜ ይፈስ ነበር:: [read more] በዚህ የተነሳም 1 ቀን የለበስኩትን ልብስ በድጋሚ አለብሰውም ነበር ከሰው ጋርም አልቀላቀልም ነበር፡በብዙ ሀኪም ቤቶች ማለትም ከሁመራ እስከ አዲስ አበባ ብዞርም ሀኪሞቹ ይሄን አይነት በሽታ ታይቶ አይታወቅም፤ ለዚህ በሽታ መድሃኒት አይገኝልህም እንደገናም አጥንትህ ስለተጎዳ ሸክም እንዳትሸከምበት ሸክም ከተሸከምክበት ይሰበራል  ነበር ያሉኝ፡፡ በተጨማሪ አራቱን ዓመት ሙሉ ምግብ  አልበላም ነበር፡፡ በዚህ የተነሳም ልቤ ደክሞ ነበር፡፡ከዚህ ሁሉ ስቃይ በኋላ ወደ ወንቅ እሸት ገዳም ስመጣ ገና ጢስ አባይ ስደርስ ለ4 ዓመት ሙሉ ምግብ ሲዘጋኝ የነበረው በሽታ ለቀቀኝ እና ወደ ወንቅ እሸት እየመጣሁ መንገድ ላይ  እያለሁ  ጢስ አባይ ስደርስ እንጀራ በላሁ፡፡ከዚያም ወደ ገዳሙ መጥቸ በመጠመቅ በህክምና‹‹ ይሰበራል አጥንቱ ተጎድቷል፤መድሃኒት የለውም ››የተባለው እግሬ ዛሬ በአባ ዮሐንስ ተስፋ ማርያም ጸሎት ሙሉ በሙሉ ተፈውሸ እንዲህ እንደ እንቦሳ እዘላለሁ በማለት በአውደ ምህረቱ ላይ እየዘለለ በደስታ የምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ [/read]

Leave a Reply