መመገብና ውኃ መጠጣት እንኳን አትችልም ነበር

አቶ እንዳወቅ አታሎ እባላለሁ፡፡ የመጣሁት ከባሕር ዳር ከተማ ከቀበሌ 07 ሲሆን ልጄ ትሕትና እንዳወቅ ትባላለች፤ በድንገት ታማ ሰውነቷ በሙሉ ሽባ ሆኖ መንቀሳቀስ እና መውጣት መግባት ይቅርና ምግብ መመገብና ውኃ መጠጣት እንኳን አትችልም ነበር፡፡ እኔም ተአምረኛነቱን ስለማውቅ ወደ ወንቅ እሸት ቅዱስ ገብርኤል አንድነት ገዳም ይዣት መጣሁ፡፡ በወንቅ እሸት ገዳም ለሁለት ሳምንት በማስጠመቅ ብቻ ልጄ ዳነችልኝ፡፡ አሁን እንደ ማኛውም ሰው እየወጣች እየወረደች ጤነኛ ሆና ትገኛለች፡፡ ልጄን ለፈወሰልኝ ለአምላከ ቅዱስ ገብርኤል ለኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይግባው፡፡

Leave a Reply